Wednesday 19 June 2019

በማስታወቂያ ላይ ግደለሽነት ለምን አስፈለገ?


       ማስታወቂያ   እጅግ  በጣም  ብዙ  ጠቀሜታዎች  ያሉት  በሀገር ደረጃ ፣በክልል፣ በወረዳ  እንዲሁም በሌሎችም ጭምር  ጥቅሞች የሚያስገኝ ማለት ነው።ይህም ሲባል  አንድን ምርት፣ አገልግሎት፣ እቃም  ሊሆኑ ይችላል የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም  ለደንበኞች  ማቅረብ  ማለት ነው።በአብዝሀኛው ማስታወቂያዎችን  ስንመለከታቸው  ሲተላለፉ   ሁሉንም የመገናኛ  ዘዴዎችን ያማከሉ ናቸው።  ከእነዚህም ወስጥ ቴሌቭዥን ሬድዮ  ፣በራሪ ወረቀቶች የፁሁፍ ሰሌዳ ፣የማስታወቂያ ሰሌዳ ፣በተለያዩ የመኪና መቆሚያ ቦታዎች ላይ ፣በመብራት ግንዶች እንዲሁም በድርጅቶች በር ላይ የተለጠፉ ናቸው።
                 
       ይህም በሚሆንበት  ጊዜ  ማስታወቂያ ሲሠራ  መቼም ሰሪው ወይም  ማስታወቂያ እንዲሠራለት የሚፈልገው  ሠው እንደት መስራት  እንዳለባቸው  ያውቃሉብየ አምናለሁ።ነገር  ነገር ግን እሚስተዋወቀው ምርት ወይም አገልግሎት  ምን ያክል ለተጠቃሚዎች አመርቂ ነው እሚለው  ላይ  ትኩረት አለመስጠታቸው ነው ።በሌላ መንገድ ደግሞ  ውጭ ላይ የሚለጠፉ ማስታወቂያዎች ላይ በጣም ብዙ  ግደለሽነት አለ  ምሣሌ:- ትኩረት አለመስጠት፣  አዳዲስ መንገዶችን አለመጠቀም ፣ደንበኞች እሚያወዛግብ የማስታወቂያ አይነት በመጠቀም ነው።
                  
      ብዙ ጊዜ ውጭ በሚለጠፉ   ፣በጋዜጣ፣ በመፅሔት በቴሌቭዥን  ማስታወቂዎች  ላይ   በጣም ብዙ ችግር ይታይባቸዋል።እያንዳንዱ  ስንመለከት  ጥራት የሌለው፣ የአካባቢን ገፅ የሚያበላሹ ማለትም የተቀደዱ(የተቦጫጨቁ) ፣አድሬስ የሌለው በጥቅሉ በጣም ብዙ  ስህቶችን እናገኛለን። ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ እቃው የሌለውን ጥራት በማጋነን የሚሰጠው ጥቅምናማስታወቂያ በጭራሽ  እማይገናኙ ናቸው።
በሌላ መልኩ  ደግሞ  አማርኛ  ማስታወቂያ ለመስራት ብዙ ጊዜ የእንግሊዝኛ ቃላቶችን   በመጠቀም  ደንበኞችን እያወዛገቡ ይታያሉ።
                  
     መፍትሔ ሊሆን የሚችለው  ግደለሽነትን   በማስወገድ ማስታወቂያ ሲሠራ  አዳዲስ ፈጠራዎችን  መጠቀም ደንበኞችን ባማከለ ፣ጥንቃቄ በተሞላበት ቢሠራጥሩ ነው። የአካባቢ ገፅታ የሚያበላሹትን ማስወገድ(መቀየር) መቻል አለባቸው። ከዚያም በተጨማሪም ማስታወቂያው  አድራሻ ሊኖረው ይገባል። በቪድዎ  ከሆነ ጥራት ሊኖረው ይገባል። በፅህፈት ከሆነ ስርአቱን ያልጠበቀና የተንዛዛም   መሆን  የለበትም።


No comments:

Post a Comment