Sunday 30 June 2019

የኦሮሚያ አለም አቀፍ ባንክ ማስታወቂያ ክፍተት


                       

             በሀገራችን  ኢትዮጵያ በአሁኑ ሠአት  ዘርፈ ብዙ የማስታወቂያ አይነቶች እየተስፋፉ ይገኛሉ።ከነዚህም ውስጥ በትላልቅና በትናንሽ የአገልግሎት ተቋማት ፊት ለፊት ላይ  የሚለጠፉ ናቸው።እነዚህም  ተለጥፈው ብዙ ጊዜ ሊቆዩና ላይቆዪም ይችላሉ።
     
         
 በቀጣይም  የምናየው በአንድ ትልቅ የአገልግሎት ሰጭ ተቋም  ላይ ያየሁትን የማስታወቂያ  ስህተትና  እንዲሁም መስተካከል ያለበትን ነገር ነው። ማስታወቂያውም  የኦሮሚያ  አለም  አቀፍ ባንክ ነው።ክፍተቱን ለመረዳት   የማስታወቂያውን ምስል ከታች ይመልከቱ።
             

ስለዚህ  ማስታወቂያዉን  በደንብ ስንመለከተው  እሚስተካከል  ስህተት አለው።ምክንያቱም  በትግርኛ ቋንቋ  ላይ  ኢንተርናሽናል ተብሎ አይፃፍም። በመቀጠልም "ኢንተርናሽናል" የሚለው ቃል እንግሊዝኛ  እንጅ  አማርኛም ሆነ  ትግርኛ ቃል አይደለም።የሀገር ውጭ  ቋንቋ መጨረሻ መምጣት እያለበት  መካከል ላይ ይገኛል። በተጨማሪ ደግሞ  ሁሉም ቋንቋ  ላይ  ኢንተርናሽናል  ይላል  ምኑን ከምኑ መለየት ይቻላል?
     

         የዚህን  ማስታወቂያ ስህተት በመረዳት  ወደ  ትክክለኛው  የማስታወቂያ አፃፃፍ ስርአት ማስኬድ ይቻላል።መፍትሔውም:-  በትግርኛ ኢንተርናሽናል የሚለውን  በመተው  ዓለምለኸዊ በሚለው  ማስተካከል እንዲሁም  አማርኛው ላይ  "አለም አቀፍ " በሚለው ይስተካከል። በይበልጥም በሚከተለው  ቢስተካከል  መልካም ነው።
     
         ባንኪ  ዓለምለኸዊ  ኦሮሚያ   .
ኦሮሚያ  አለም አቀፍ  ባንክ  .
       OROMIA  INTERNATIONAL  BANK  S.C

                        ለመረጃነት ምስሉን  ይመልከቱ።


                              
  
       



       


No comments:

Post a Comment