Monday 1 July 2019

ከዘመን ጋር የዘመኑት የልብስ ማስታወቂያ በኢትዮጲያ



  
      ማስታወቂያ አዳዲስ ነገሮችን ለደንበኞች የት እንደሚገኝ መረጃ ማድረስ ነው፡፡ደንበኞች ደግሞ የሠሙትን ወይም ያዩትን ማስታወቂያ አድራሻ ይዘው ምርቱ ካለበት ቦታ በመሄድ ገዝተው መጠቀም ነው፡፡ነገር ግን ተጠቃሚዎች ይሄ ምርት በታዋቂ ሰዎች መተዋወቁ በጣም አሪፍ ይመስላቸውና ወደ ተግባሩ ገብተው ሲጠቀሙት እናያለን፡፡ ለምሳሌ እንይ ዘመን እየዘመነ ሲሄድ የእኛ የአለባበስ እስታይልም ይዘምናል፡፡

      ይህ ማለት የዘመኑ ፋሽን ልብሶችን መግዛት ፋሽኖች የሚባሉት ደግሞ የምዕራባውያን ባህሎዎች ናቸው፡፡እነዚህን ባህሎዎች እኛ መከተላችን የእኛ ባህል ላይ ተፅዕኖ ማሳደሩ በተግባር እየታየ ነው፡፡ ታድያ እኛ ዘመን እያልን እምናጠፋ ከሆነ "የራሷ አሮባት የሰው ታማስላለች" እንደሚባለው እኛም የራሳችንን ትተን የሠው እንፈልጋለን፡፡ምንም ይሁን ምን ይህ የፋሽን ማስታወቂያ በእኛ ላይ ተፅዕኖ አለበት፡፡ስለዚህ ሁላችንም እናውቀዋለን፡፡


ታድያ የራሳችንን ባህል ከማጥፋት የእኛን የሆነ ነገር መከተል ተገቢ ይሆናል፡፡ምንአልባት ይሄንን ፋሽን መከተል እንደ ዘመናዊነት ሆኖ ያገለግላል፡፡ለምሳሌ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ብናይ ተማሪዎች ለምርቃት የሚገዙት ፋሽን ልብስ ከሀገራቸው አለባበስ ይልቅ የውጭ አለባበስ እስታይለል መልበስ ይፈልጋሉ፡፡ እነሱ ይሄንን አደረጉ ማለት ነገ የእነሱ ልጆች ደግሞ በፍፁም ተመልሳችሁ ባህላችሁን ተከተሉ ቢባሉ ከመመለስ ይልቅ መሳለቂያ ያደርጋል፡፡ስለዚህ አሁኑኑ ከአጉል ፋሽን ተመልሰን የራሳችንን በፋሽን እንደገና ማደስ ለልጆቻችን ማስተማር፣መንገር ባህላችን እንድህ ነበር እያልን ማስገንዘብ አንድ ተገቢ ቁም ነገር ነው፡፡


     ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ ታሪካዊ ቦታዎችን፣ቅርሶችን ማስጎብኘት እንድንከባከባቸው ማድረግ የእኛ ሀላፊነት መሆኑን አውቀን ከባህል ያልራቀ ትውልድ አፍሪዎች መሆን አለብን፡፡ በአጠቃላይ ማስተላለፍ የፈለኩት ነገር እነዚህ የፋሽን ልብሶች ምርት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በዚያውም ማስታዎቂያው እየጨመረ ስለመጣ ቢያንስ እንኳን ሙሉ በሙሉ የእኛን አለባበስ ሳንረሳ አንዳንድ ጊዜ ፋሽን መጠቀም ይቻላል፡፡


No comments:

Post a Comment